በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ኢንተር ሚላን ባርሴሎናን 4ለ3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
የኢንተር ሚላንን የማሸነፊያ ግቦች ማርቲኔዝ ፣ ካልሀኖግሉ ፣ አቼርቢ እና ፍራቴሲ አስቆጥረዋል።
ለባርሴሎና ግቦችን ኤሪክ ጋርሽያ ፣ ዳኒ ኦልሞ እና ራፊንሀ ከመረብ አሳርፈዋል።
ኢንተር ሚላን በድምር ውጤት ባርሴሎናን 7ለ6 በማሸነፍ ለሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።
ኢንተር ሚላን ባለፉት ሶስት አመታት ለሁለተኛ ጊዜ ለአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ መድረስ ችለዋል።
አሰልጣኝ ሲሞኒ ኢንዛጊ ቡድኑን ከተረከቡ በኃላ ለሁለተኛ ጊዜ ቡድኑን በሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ አብቅተዋል።
በሙኒክ በሚደረገው የፍፃሜ ጨዋታ ድል የሚቀናቸው ከሆነ አራተኛ የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫቸውን ማሳካት ይችላሉ።
ከ ኢንተር ሚላን በላይ ብዙ የሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ መድረስ የቻለው ክለብ ሪያል ማድሪድ ብቻ ነው።
የሴርያው ክለብ ኢንተር ሚላን የፍፃሜ ጨዋታውን ከፒኤስጂ እና አርሰናል አሸናፊ ጋር ሙኒክ ላይ የሚያደርግ ይሆናል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
