(ይትባረክ ዋለልኝ)
አስራ ሰባተኛው የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ፕሬስ የመፅሐፍ ዓውደ ርዕይ እና ሽያጭ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ግቢ ውስጥ ይካሄዳል፡፡ ለ 7 ቀን በሚቆየው በዚህ የመፅሐፍ ዓውደ ርዕይ እና ሽያጭ ላይ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ፕሬስ; የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ : ጃፋር መፅሐፍ እና በርካታ አሳታሚዎችና አከፋዮች
በቅናሽ ዋጋ መፅሐፍቶችን ይዘው በዓውደ ርዕዩ ላይ ይጠብቋችኃል::
በዚህ የመፅሐፍ ዓውደ ርዕይ ላይ አዳዲስ መጽሐፍት ይመረቃሉ:ውይይቶች ይካሄዳሉ:ለህፃናት የንባብ ፕሮግራም ይካሄዳል::እንዲሁም ከገበያ የጠፉ እና በርካታ መፅሐፎች : የህፃናት መፅሐፎች: የሐይማኖት መፅሃፎችን ጨምሮ ሁሉንም በአንድ ስፍራ ያገኛሉ! ሁላችሁም እንድትገኙ ተጋብዛችኃል!!
እስከ እሁድ ድረስ ያለውን ፕሮግራም ፎቶው ላይ ያገኙታል::
ቦታ በዋናው ግቢ ስድስት ኪሎ ካምፓስ!
