ከማህበረሰቡ ከሚቀርቡለት የተበደልን አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ እኔን አይመለከቱም

Date:

በህግ የተሰጠኝ ሃላፊነት የግልም ሆነ የመንግስት ድርጅቶች ማህበረሰቡ ላይ የሚፈፅሟቸውን አስተዳደራዊ በደሎች የተመለከቱ አቤቱታዎችን ተቀብሎ በመመርመር የተበዳዮችን እምባ ማበስ ነው የሚለው ተቋሙ፤ ነገር ግን ብዙ ጊዜ የሚቸገርበት ጉዳይ ማህበረሰቡ ወደ እምባ ጠባቂ ተቋም ማምጣት ያለበትን ጉዳይ አለማወቅ እንደሆነ ነግሮናል፡፡

በዚህ ምክንያት አጠቃላይ አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ አይመለከቱንም ብለን የምንመልሳቸው ናቸው ያሉን የተቋሙ ምክትል እምባ ጠባቂ ዶክተር የኔነህ ስመኝ ናቸው፡፡

በህዝብ ምርጫ የተቋቋሙ ምክር ቤቶች በህግ አውጪነታቸው የሚሰጧቸው ውሳኔዎችን፤ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያሉና ውሳኔ ያገኙ ጉዳዮች፤በዋና ኦዲተር እየታዩ ያሉና ውሳኔ የተሰጣቸው ጉዳዮች፤ በመከላከያ ሰራዊትና በፀጥታ አካላት የሚወሰኑ ውሳኔዎችን የተመለከቱ ጉዳዮችን ተቋሙ መቀበልም ይሁን መፍትሄ ማሰጠት እንደማይችል እወቁት ተብሏል፡፡

የማይመለከተንን አቤቱታ በመቀበል ከተጠመድን የሌሎች አቤት ባዮችን ጊዜ ይሻማል የሚሉት ምክትል ዋና እምባ ጠባቂው የሚቀርቡና የማይቀርቡ ጥያቄዎችን ለማህበረሰቡ የማስረዳት ሃላፊነት ብለውናል፡፡

ተቋሙ ከተጠቀሱት ውጭ የሆኑ ማንኛውም አስተዳደራዊ በደሎችን ተቀብሎ በማጣራት በዳይና ተበዳይ ጉዳዩን በስምምነት እንዲጨርሱት ማድረግ የመጀመሪያው ስራ መሆኑን የሚያስፈዱት ዶክተር የኔነህ፤ በዚህ መንገድ ማለቅ ካልቻለ ነው ወደ ቀጣዩ እርምጃ የሚኬደው ነገር ግን ቅሬታ የቀረበባቸው ተቋማት የፈጠሩትን ችግር ለማስተካከል ፍቃደኛ አለመሆን የስራው እንቅፋት ነው ይላሉ፡፡

ከሚቀርቡለት አቤቱታዎች በተጨማሪ ተቋሙ በራሱ ተነሻሽነት መፍትሄ ሊያገኙ ጉዳዮችን ይገባል የሚላቸውን ጉዳዮች እንዲያጣራና መፍትሄ እንዲሰጥም ሃላፊነት ተሰጥቶታል ተብሏል፡፡

በተቋሙ አሰራር መሰረት አጣርቶ ይስተካከሉ በማለት ለተቋማት የሚልካቸው ምክረ ሃሳቦች በ30 ቀናት ውስጥ ምላሽ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡

ወደ እምባ ጠባቂ የሚቀርቡ አቤቱታዎችም ከ6 ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እልባት እንደሚሰጣቸው ከሃላፊው ሰምተናል፡፡

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...