ከሰሞኑ እስራኤል ሶስት ጋዜጠኞችና ሶስት የተረድኦ ድረጅት ሰራተኞች መግደሏ የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ

Date:

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበርያ ኤጀንሲ (ኦቻ) መረጃ መሰረት ከገባ ዘጠኝ ቀናት ብቻ ባስቆጠረው የኤፕሪል ወር እስራኤል አንድ የኤምኤስኤፍ አባልና ሁለት የፍሊስጤም ቀን ጨረቃ ማህበር ሰራተኞችን መግደሏን ገልፆል።

ይህም ከጥቅምት ሰባቱ ጥቃት ወዲህ እስራኤል በጋዛ ላይ በፈፀመቻቸው የተለያየ መልክ ያላቸው ጥቃቶች የተገደሉት የተራድኦ ድርጅት ሰራተኞች ቁጥር 412 አድርሶታል።

ኦቻ አክሎም ሶስት ፍልስጤማውያን ጋዜጠኞችም ባለፈው አንድ ሳምንት መገደላቸውን ያስታወቀ ሲሆን ኤፕሪል 6ና 7 በካንዮንስ በተፈፀሙ ሁለት ጥቃቶች አንዲት ኢስላም ማክዳድ የተሰኘች እንስት ፍሊስጤማዊ ጋዜጠኛን ጨምሮ ሶስቱ ጋዜጠኞች ተገድለዋል። የጋዜጠኞቹን ህይወት በቀጠፉት ጥቃቶች ሴቶችና ህፃናት የሚገኙባቸው በርካታ ሰላማውያን ሰዎች መገደላቸውም ተዘግቧል።

የነዚህ ሶስት የሚድያ ሰዎች ግድያ ደግሞ በአጠቃላይ በእስራኤል ጥቃት በጋዛ የተገደሉት ጋዜጠኞች ቁጥር 208 አድርሶታል ተብሏል።

በሚሊዮን ሙ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...