በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበርያ ኤጀንሲ (ኦቻ) መረጃ መሰረት ከገባ ዘጠኝ ቀናት ብቻ ባስቆጠረው የኤፕሪል ወር እስራኤል አንድ የኤምኤስኤፍ አባልና ሁለት የፍሊስጤም ቀን ጨረቃ ማህበር ሰራተኞችን መግደሏን ገልፆል።
ይህም ከጥቅምት ሰባቱ ጥቃት ወዲህ እስራኤል በጋዛ ላይ በፈፀመቻቸው የተለያየ መልክ ያላቸው ጥቃቶች የተገደሉት የተራድኦ ድርጅት ሰራተኞች ቁጥር 412 አድርሶታል።
ኦቻ አክሎም ሶስት ፍልስጤማውያን ጋዜጠኞችም ባለፈው አንድ ሳምንት መገደላቸውን ያስታወቀ ሲሆን ኤፕሪል 6ና 7 በካንዮንስ በተፈፀሙ ሁለት ጥቃቶች አንዲት ኢስላም ማክዳድ የተሰኘች እንስት ፍሊስጤማዊ ጋዜጠኛን ጨምሮ ሶስቱ ጋዜጠኞች ተገድለዋል። የጋዜጠኞቹን ህይወት በቀጠፉት ጥቃቶች ሴቶችና ህፃናት የሚገኙባቸው በርካታ ሰላማውያን ሰዎች መገደላቸውም ተዘግቧል።
የነዚህ ሶስት የሚድያ ሰዎች ግድያ ደግሞ በአጠቃላይ በእስራኤል ጥቃት በጋዛ የተገደሉት ጋዜጠኞች ቁጥር 208 አድርሶታል ተብሏል።
በሚሊዮን ሙ
