የአፍሪካ ሕብረት በቅኝ ግዛት ካሳ ዙሪያ በአውሮፓ ሕብረት ላይ ጫና ሊያሳድር ይገባል ተባለ

Date:

በአፍሪካ ሕብረት የዲያስፖራ ጉዳዮች ክፍል ኃላፊ አንጄላ ናአ አፎሌ ኦዳይ ለአውሮፓ ሕብረት በአፍሪካ ላይ ለፈጸመው ቅኝ ግዛት እና ለአትላንቲክ የባሪያ ንግድ ካሳ እንዲከፍል ጫና ሊደረግበት እንደሚገባ ተናገሩ።

ኃላፊው ለእንግሊዝ ሚዲያ በሰጡት መግለጫ በአውሮፓና በሌሎችም ቦታዎች የቀኝ ዘመም እንቅስቃሴ እየጨመረ ቢመጣም አፍሪካ ካሳ መጠየቅ አለባት ብለዋል። “የተለያዩ አመቺ ያልሆኑ ጉዳዮች ቢኖሩም የካሳ ክፍያን ለማንሳት ከዚህ የተሻለ ጊዜ የለም” ሲሉ ተደምጠዋል ።

በየካቲት ወር የተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤም የማካካሻ ፍትሕ እና በአህጉሪቱ ላይ ለተፈፀመው ዘር ተኮር አድልዎ መፍትሔ መፈለግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ሕብረቱ ይህን ግብ ለማሳካት ዲፕሎማሲያዊ ጫና ከመፍጠር ባለፈ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች ሕጋዊ እርምጃ መውሰድን እንደ አንድ ስትራቴጂ እንደሚመለከት ቀደም ሲል አስታውቋል።
በዚህ ረገድ ኃላፊው የአፍሪካ ሕብረት ከአውሮፓ ሕብረት እንዲሁም ከካሪቢያን አገራት ጋር የሚያደርገው ትብብር ካሳን በተመለከተ የተቀናጀ አቋም ለመፍጠር ጠቃሚ መንገድ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...