ከ27 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በቁጥጥር ስር ዋለ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ በቃሊቲ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ቱሉ ዲምቱ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 27 ነጥብ 75  ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በቁጥጥር ስር የዋለው ጥፍጥፍ  ወርቅ ከአንድ ወር በላይ ክትትል ሲደረግበት መቆየቱን የጉምሩክ ኮሚሽን የሕግ ተገዥነት ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ ተናግረዋል፡፡

ጥፍጥፍ ወርቁን በህገወጥ መንገድ በተሽከርከሪ አካል ውስጥ ደብቀው ሲያዘዋውሩ የነበሩ ሶስት ተጠርጣሪዎችና ሁለት ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል፡፡

የኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከፋና ዲጂታል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...