ክቡር ኮሌጅ በ2013 ዓ ም ዕውቅና አግኝቶ የተመሰረተ የAABS አባል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ሲሆነ በኢትዮጵያ የ2026 የአፍሪካ ቢዝነስ ስኩል ማህበር AABS አመታዊ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ያስተናግዳል።
ለኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ እና በአፍሪካ የትምህርት ደረጃ እያደገ ላለው ትልቅ ምዕራፍ፣ የ2026 የአፍሪካ ንግድ ትምህርት ቤቶች ማኅበር (AABS) ዓመታዊ ኮንፈረንስ እንድታዘጋጅ ኢትዮጵያ ተመረጠች ዝግጅቱ ከግንቦት 12 እስከ 14 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን ከ150 በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ዳይሬክተሮች እና የአለም አቀፍ አካዳሚክ መሪዎች ከመላው አፍሪካ እና ከዓለም አቀፍ ይሳተፋሉ።
የአፍሪካ የንግድ ትምህርት ቤቶች ማህበር (AABS) ማነው?
እ.ኤ.አ. በ2005 የተመሰረተ እና መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው የአፍሪካ የንግድ ትምህርት ቤቶች ማህበር (AABS) በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ ትምህርት ጥራት፣ተፅእኖ እና አግባብነት ለማሳደግ የተቋቋመ መሪ የፓን አፍሪካ ኔትወርክ ነው። በአፍሪካ የንግድ ትምህርት ቤቶች ፈጠራን፣ አመራርን እና የላቀ ብቃትን በእውቀት ሽግግር፣ በትብብር፣ በአቅም ግንባታ እና በፖሊሲ ዙሪያ አበክሮ ይሰራል።
ለምን ኢትዮጵያ? ለምን አዲስ አበባ?
ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ ቢዝነስ ስኩልስ ማህበር /AABS Connect Conference 2025/ በሃገራችን ብቸኛ አባል ሲሆን
ኮሌጁ ከሁለት ዓመት በፊት የሚጠበቅበትን መስፈርት አሟልቶ ያቀረበዉ ጥያቄ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች የተሻለ ተቀባይነት አግኝቶ የ2026 የማህበሩ ዓመታዊ ጉባኤ በክቡር ኮሌጅ አዘጋጅነት ኢትዮጲያ እንድታካሄድ ተመርጣለች።
እንዲሁም ሃገራችን በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለትምህርት ማሻሻያ እና ለውጥ ጠንካራ ቁርጠኝነት በመንግስት እና በከተማ አስተዳደሩ የሚመራ የኮንፈረንስ እና የአካዳሚክ ቱሪዝምን ለማዳበር የተተገበሩ ዉጤታማ ስራዎች፣
የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ዲፕሎማሲያዊ፣ የባህል የአፍሪካ ህብረት እና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት መገኛ መሆኗ፣
አዲስ አበባ የተሻሻለ የመሰረተ ልማት፣ እና የመስተንግዶ አገልግሎት ወደ ዘመናዊ፣ ከተማነት መቀየሩ ለአለም አቀፍ ዝግጅቶች ተመራጭ መዳረሻ አድርጓታል። ከተማዋ የኮንፈረንስ እና የባህል ቱሪዝም ማዕከል ሆና ያላት ስም እየጨመረ መምጣቱ ለምርጫዋ ትልቅ አስተዋፅዖ አድርጓል።
የዓለም አቀፍ ጉባኤ በሃገራችን መዘጋጀት ያለው ጠቀሜታ፣
ክቡር ኮሌጅ – በኢትዮጵያ እያደገ ያለው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደ አስተናጋጅ ተቋም ይህንን ትልቅ ጉባኤ በማዘጋጀት ግንባር ቀደም ሆኖ ከባለድርሻ አካላት እየሰራ ነው። ኮሌጁ ከሀገራዊ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች እና አህጉራዊ ግቦች ጋር ተጣጥሞ አግባብነት ያለው፣ተፅዕኖ ያለው እና ስራ ፈጣሪ ትምህርት ለመስጠት ቁርጠኛ ነው።
መርሃ ግብሩ በትብብር ከትምህርት ሚኒስቴር፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር ተቀናጅቶ የሚካሄድ ነው ።
👉በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ/አለም አቀፍ ተቋማት መካከል የእውቀት ሽግግር;
👉በምርምር ፣በፈጠራ ፣በፋኩልቲ ልማት እና በስራ ፈጠራ ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ፤
👉የኢትዮጵያን የንግድ ተቋማት ከከፍተኛ ትምህረት ተቋማት ጋር በጋራ የሚሰሩበትን በጎ አጋጣሚ መፍጠር።
👉በሃገራችን የኮንፍረስ ቱሪዝም ተጠቃሚነትን በማሳደግ ለዓለም በጎ ገፅታዋን ማሳደግ፣
ክቡር ኮሌጅ ሰፊ አገራዊ ተሳትፎን እና የረዥም ጊዜ በጎ ተጽኖን ለማረጋገጥ ከመንግስት እና ከግል ተቋማት – የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና፣ ዩኒቨርሲቲዎች እና የንግድ ልማት ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ ለመስራት እና ዉጤታማ ጉባኤ ለማካሄድ ጥሪ ያቀርባል።
