ከ3 ወር ነፍሰጡሯ እናት ሆድ 8.9 ኪሎ ግራም የሚመዘን እብጠት ተወገደ

Date:

መገኛው በትግራይ ክልል ሓውዜን ከተማ ያደረገው ፍረ ሰማእታት አንደኛ ደረጃ ሆስፒታል ከአንዲት እናት ሆድ 8.9 ኪሎግራም የሚመዘን እብጠት በቀዶ ህክምና ማስወገድ መቻሉን ቀዶ ህክምናውን የሰራውና የሆስፒታሉ ባልደረባ የሆነው ተክለማርያም ተስፋማርያም ተናግረዋል።

እንደ ሞያተኛው ገለፃ ከሆነ ቀዶ ህክምናው የተደረገላት እናት የ32 ዓመት ሴት ስትሆን ከቆራሮ ጤና ጣብያ በሪፈር የመጣች ነች ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪም እብጠቱ ለአስር ዓመታት ያህል በሆዷ የቆየ መሆኑም ተገልፆል።

ወጣቷ ቀዶ ህክምናው በምታደርገበት ወቅት የሶስት ወር ነፍሰጡር የነበረችም ሲሆን ከቀዶ ህክምናናው በኃላም ፅንሱ በጥሩ ሁኔታ ውስጥ ይገኛል ተብሏል።

የቀዶ ህክምናው ሂደቱ ለ3 ሰዓታት ያህል የዘለቀ ነበር የተባለ ሲሆን በቀዶ ህክምናው የተወገደው እብጠት ለተጨማሪ የካንሰር ምርመራ ወደ አይደር ሪፈራል ሆስፒታል ተልኮ በምርመራ ውጤቱም ከካንሰር ነፃ መሆኑ መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...