ከ400 ሺህ በላይ ቱሪስቶች አፋርን ጎብኝተዋል – የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ

Date:

በ2017 በጀት ዓመት 404 ሺህ የሚሆኑ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስቶች የአፋር ክልልን መጎብኘታቸውን የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ገልጿል።

በክልሉ የመዓድን፣ ፍል ውኃ እና ሌሎችም ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶችን ለማልማት እና የቱሪስት ፍሰቱን ለማሳደግ በተሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎች ትልቅ ለውጥ መገኘቱን የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አብዱ መሃመድ ገልፀዋል።

የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ መዳረሻዎችን በማልማት የውጭ እና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ማድረግ መቻሉን አቶ አቡዱ መሃመድ አንስተዋል።

በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት 4 ሺህ 300 የውጭ ቱሪስቶች ክልሉን የጎበኙ ሲሆን በዚህም 8.6 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ነው የተናገሩት፡፡

በአፋር ክልል የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስፋትና የዘርፉን እንቅስቃሴ በማጠናከር ረገድ ትልቅ ስኬት እየተመዘገበ መሆኑም አክለው ገልጸዋል።

በቀጣይም ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት በመስጠት በርካታ ስራዎችን ለመስራት መታቀዱን አቶ አብዱ መሃመድ አንስተዋል።
EBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...