በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስድስት ወራት ውስጥ 19 ሺሕ 800 ጋብቻዎች እና 5 ሺሕ 805 ፍቺዎች መመዝገባቸውን የከተማዋ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታውቋል።
የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጥጋቡ ሹመይ እንዳሉት ለተለያዩ ማኅበራዊ አገልግሎቶች የፍቺ ማስረጃ እንደ ቅድመ ሁኔታ መጠየቁ የዘገዩ ፍቺዎች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡
በዚህም ከተመዘገቡት ፍቺዎች መካከል 1 ሺሕ 750 ያህሉ ፍቺ በተፈጸመ በ30 ቀናት ውስጥ የተመዘገቡ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 695ቱ ደግሞ ዘግይተው የተመዘገቡ መሆናቸውን የዘገበው ኤ ኤም ኤን ነው ።
ይህም የምዝገባ ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከሁለት ሺህ በላይ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።
