እውነት ስላለን እና በቅንነት ህዝባችንን ማገልገል ስለምንፈልግ ማንም ድጋፍ ባይሰጠንም እውነተኛ ፈራጅ ስለሚያይ ማንም አያሸንፈንም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ፡፡
ህወሓት በኤርትራ ወታደር እንዳይዘረፍ ስንጠብቀው አማራ ክልል ገብቶ ያደረገው ነገር አሳፋሪ ነው ሲሉ ኮንነዋል፡፡
ቡድኑ በአማራ ክልል ውስጥ ፋብሪካ ማፍረሱን፤ ትምህርት ቤት ማቃጠሉን እና ባንክ መዝረፉን አንስተዋል፡፡
የትግራይ ሀይል ይህንን በሚያደርግበት ወቅት ግን መከላከያ ሰራዊት መቀሌን ያለምንም ጥፋት ጠብቋታል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ኢትዮጵያን ያላስቀደመ ለጊዜያዊ ድል እና ለሚዲያ ጨዋታ የሚደረግ የፖለቲካ ስብዕና በዘላቂነት በህዝብ እና በታሪክ ላይ ጉዳት ያመጣል ሲሉ ለምክር ቤት አባላት ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ በፕሪቶሪያ ስምምነት ወቅት የተስማማንባቸው ጉዳዮች ናቸዉ የፀብ መነሻ እየሆኑ ያሉት ያሉ ሲሆን፤ ይህ ሁኔታ ለማንም አይጠቅምም ብለዋል፡፡
