የሎጆችና ሬስቶራንቶች ደረጃ አሰጣጥ ሥርዓት ሊጀመር ነው

Date:

የቱሪዝም ሚኒስቴር ቀደም ሲል በሆቴሎችና ሪዞርቶች ላይ ብቻ ሲካሄድ የቆየውን የደረጃ ምዘና ሥራ፣ ሎጆችንና ሬስቶራንቶችን ጭምር እንዲያካትት የሚያስችል አዲስ ሀገራዊ መመዘኛ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

ይህ አዲስ የደረጃ አሰጣጥ ሥርዓት አገሪቱ ለቱሪዝም ዘርፍ የምትሰጠውን ትኩረት ከፍ የሚያደርግ ሲሆን፣ የዘርፉን ጥራትና አገልግሎት ለማሻሻል ያለመ ነው ተብሏል።

የተዘጋጀው መመዘኛ በረቂቅ ደረጃ ተጠናቅቆ፣ በቀጣይነት ለባለድርሻ አካላት ውይይት ቀርቦ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል።

በሌላ በኩል፣ ከ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ አዳዲስ ሆቴሎች በተገቢው ጊዜ የደረጃ ምደባ እንዲያደርጉ የታቀደ ቢሆንም፣ የደረጃ ምደባው ሂደት ላይ ችግሮች መፈጠራቸው ታውቋል።

የተፈጠሩት ችግሮች ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች እንዳሏቸው ተጠቁሟል። አንደኛው፣ ባለሀብቶች በተያዘው ጊዜ የኮከብ ደረጃ ለመመደብ ፈቃደኛ አለመሆናቸው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ አብዛኞቹ ተቋማት የኮከብ ደረጃ ለመመደብ ብቁ ሆነው አለመገኘታቸው ነው። ይህ ደግሞ የቱሪዝም ዘርፉን ጥራት ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ላይ ፈተና እንደሚሆን ተገልጿል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...