“የሕወሓት እና የሻዕቢያ ጋብቻ በትግራይ ወጣቶች ላይ የታወጀ ሌላ የሞት ፍርድ” ወይዘሮ አረጋሽ አዳነ

Date:

የቀድሞ የሕወሓት ታጋይ ወይዘሮ አረጋሽ አዳነ፣ አሁን ላይ በሕወሓት ቡድን እና በሻዕቢያ መካከል እየታየ ያለው ትስስር ዋና ዓላማው የትግራይን ወጣት ለተጨማሪ እልቂት መዳረግ መሆኑን ገለጹ።

ሻዕቢያ የራሱን ሕዝብ ችግር መፍታት ያልቻለና በሁከት የሚኖር ድርጅት መሆኑን የጠቀሱት ወይዘሮ አረጋሽ፣ አሁን እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ለትግራይ ሕዝብ ተቆርቁሮ ሳይሆን የራሱን ጥቅም ለማስጠበቅና የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ እንደሆነ አስረድተዋል።

ሻዕቢያ ቀደም ሲል በትግራይ ውስጥ ንጹሐንን መጨፍጨፉንና ንብረት መዝረፉን ያስታወሱት የቀድሞዋ ታጋይ፣ አሁንም ጦርነቱ ትግራይ ውስጥ እንዲሆንና ከባለፈው እልቂት የተረፈውን የትግራይ ወጣት ለመጨረስ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ ኃይል ጋር አብሮ መሥራት የትግራይን ሕዝብ መካድ ብቻ ሳይሆን፣ ሕዝቡን ዳግም ለከፋ ሰብአዊ መከራና ለባዕዳን ፍላጎት መገበር እንደሆነም በጽኑ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም የሕወሓት ቡድን የሕዝብን ችግር ወደ ጎን በመተው የራሱን የሥልጣን ፍላጎት ለማርካት ከሻዕቢያ ጋር ማበሩን የትግራይ ሕዝብ ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስበዋል።

ከጥፋት ኃይሎች ጋር መተባበር በሀገርና በሕዝብ ላይ እንደመሰለፍ የሚቆጠር ወንጀል መሆኑን በመግለጽ፣ የትግራይ ወጣት ለዚህ ከንቱ የፖለቲካ ቁማር መሣሪያ እንዳይሆን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...