የማኅበራዊ ሚዲያ ጥላቻ ሴቶችና ልጃገረዶች ላይ እየተባባሰ መምጣቱ ተጋለጠ

Date:

በኢትዮጵያ ሴቶችና ልጃገረዶች በማኅበራዊ ሚዲያ በተደጋጋሚ የጥላቻ ንግግርና ማግለል እየደረሰባቸው መሆኑን አዲስ ጥናት አመለከተ።

ሴንተር ፎር ኢንፎርሜሽን ሪዚሊየንስ (ሲ.አይ.አር) የተባለ ተቋም ባካሄደው ጥናት መሰረት፣ ይህ ችግር ሴቶችን ከማኅበራዊ ተሳትፎ ከመግፋት ባለፈ በዲጂታል ዓለም ያላቸውን ደህንነት አደጋ ላይ ጥሏል።

ጥናቱ በፌስቡክ፣ ኤክስ (ትዊተር)፣ ቴሌግራም፣ ዩትዩብ እና ቲክቶክ ላይ የተደረገ ሲሆን፣ በተለይም የተለመደውን የአኗኗር ዘይቤ የሚቃወሙ ወይም በአመራር ቦታና በስፖርት ውስጥ ያሉ ሴቶች ለከፋ ትንኮሳና ንቀት እንደሚጋለጡ አመልክቷል።

ተመራማሪዎቹ ይህ የጥላቻ ንግግር በሴቶች ላይ ከሚያደርሰው የስነ ልቦና ጫና ባሻገር፣ በአጠቃላይ በሀገሪቱ ውስጥ ያላቸውን ሚናና ተሳትፎ እያደከመ መሆኑን አሳስበዋል።

በተጨማሪም ጥናቱ እንዳመለከተው በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት በስርዓተ-ፆታ ላይ ባሉ የተሳሳቱ አመለካከቶችና ማኅበራዊ ሚናዎች የተጠናወተው ነው። የፖለቲካ አለመረጋጋቶችና ግጭቶች ደግሞ የዘርንና የፆታን ጥላቻ የሚያባብሱ ሆነው ተገኝተዋል።

የሲ.አይ.አር የምርምር ኃላፊ ፌልሲቲ ሙልፎርድ “በማኅበራዊ ሚዲያ የሚፈጠረው ጥላቻ በገሃዱ ዓለምም አደገኛ ውጤት ሊያስከትል ይችላል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ጥናቱ አሁን ያሉት የይዘት ቁጥጥር ስርዓቶች ሴቶችንና ልጃገረዶችን በበቂ ሁኔታ ከመጠበቅ አንፃር ክፍተት እንዳላቸው አሳይቷል። ተቋሙ ይህ ጥናት በኢትዮጵያ የዲጂታል ምህዳር ውስጥ ያለውን አሳሳቢ ሁኔታ ለመጠቆም ያለመ መሆኑን ለካፒታል በላከዉ መግለጫ ገልጿል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...