በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሊቀመንበር አሉላ ኃይሉ ነጋ በፈቃዳቸው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የአመራር ለውጥ መገረጉ ተገልጿል።
ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፤ በምክትል ሊቀመንበርነት እና በሊቀመንበርነት ድርጅቱን ለስድስት ዓመታት የመሩት አሉላ፣ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በተካሄደው አጠቃላይ የአመራር ስብሰባ ላይ መልቀቂያቸውን አቅርበዋል ሲል ገልጿል።
አቶ አሉላ መልቀቂያ ማቅረባቸውን ለአዲስ_ስታንዳርድ አረጋግጠዋል።
አቶ አሉላ፣ “አሁን ለተጨማሪ ትግል መዘጋጀት አለብኝ፤ በትግራይ ውስጥ ኃላፊነትን በፈቃደኝነት መልቀቅ እንደ መደበኛ ነገር መታየት እና በፓርቲያችንና በትግራይ ፖለቲካ ውስጥ ባህል እንደሚሆን አምናለሁ” ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው (ፌስቡክ) ላይ አስፍረዋል።
“ሥልጣን የሥራ ቦታ ነው። ሥራ ደግሞ አድካሚ ነው፣ ስለዚህ ለሌላ ሰው ማስተላለፍ ተገቢ ነው” በማለት አክለዋል።
ፓርቲው ባወጣው መግለጫ የአሉላን መልቀቂያ መቀበሉን እና “ክንፈ ሓዱሽን አዲሱ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል” ብሏል።
