የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር – የፍቺ ቁጥርን ለመቀነስ የቅድመ የጋብቻ ስልጠና እየሰጠሁ ነው ብሏል።
ይህ የተባለው ዛሬ ለሚከበረው የቤተሰብ ቀንን አስመልክቶ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው፡፡
በዚህም ሰዎች ለፍቺ ከመዳረጋቸው አስቀድሞ ወደ ትዳርም ከመግባታቸው በፊት የተለያዩ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱና የምክር አገልግሎት እንደሚሰጣቸው ከተቋሙ ሰምተናል፡፡
ይህም ወደ ትዳር ከገቡ በኋላ የሚገጥማቸውን ችግሮች ለመፍታት ያግዛቸዋል ተብሏል፡፡
ስልጠናው የሚሰጠው ወደ ትዳር ከመግባታቸው በፊት ወደ ትዳር ከገቡ በኋላና በትዳር ላይ ሆነው የሚወስዱት እንደሆነ የተናገሩት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ሁርያ አሊ ናቸው ሲል ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
