የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ መሳይ ለተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ እና ሴራሊዮን ጋር ለሚያከናውናቸው የዓለም ዋንጫ ማጣርያ 7ኛ እና 8ኛ ጨዋታዎች ዝግጅት አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ26 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርበዋል።

በግብ ጠባቂነት – አቡበከር ኑራ፣ ቢኒያም ገነቱ እና ፍሬው ጌታሁን ተመርጠዋል።

በተከላካይ መስመር – አስራት ቱንጆ፣ ያሬድ ካሳዬ፣ ረመዳን የሱፍ፣ ሱለይማን ሃሚድ፣ አህመድ ረሺድ፣ ራምኬል ጀመስ፣ ንጋቱ ገብረስላሴ፣ ያሬድ ባየህ እና ምኞት ደበበ ተካተዋል።

በአማካኝ ስፍራ – ሃብታሙ ካሳዬ፣በረከት ወልዴ፣ሃይደር ሸረፋ፣አብዱልከሪም ወርቁ፣ቢኒያም በላይ፣ከነአን ማርክነህ እና ወገኔ ገዛሃኝ ይገኙበታል።

በፊት መስመር ላይ – ቸርነት ጉግሳ፣ በረከት ደስታ፣ ኪቲካ ጅማ፣ ዳዋ ሁቴሳ፣ አህመድ ሁሴን፣ መሃመድ አበራ እና ቢኒያም አየነ በአሰልጣኙ ጥሪ የቀረበላቸው ተጫዋቾች ናቸው።

ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች እስከ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት ድረስ በጁፒተር ሆቴል እንዲሰባሰቡ ጥሪ የቀረበ ሲሆን በቀጣይ ቀናት ወደ አዳማ በማምራት ዝግጅታቸውን እንደሚጀምሩ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...