የተለያዩ የኮንስትራክሽን ግብዓቶች በሀገር ውስጥ ምርት እየተካሁ ነው

Date:

የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ የኮንስትራክሽን ግብዓት ልማት አቅርቦት ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጠንክር መኩሪያ ከኤፍ ኤም 97.1 ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከውጭ የሚገቡ የኮንትራክሽን ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኮንስትራክሽን ግብዓቶችን 80 በመቶ በሀገር ውስጥ ለመተካት  የ10 ዓመት እቅድ አቅዶ እየሰራ እንደሆነም አቶ ጠንክር መኩሪያ ተናግረዋል፡፡ በ2017ዓ.ም እቅድ መሰረት 45 በመቶ የነበረው የሀገር ውስጥ የኮንስትራክሽን ግብዓት ምርት ከ8 በመቶ በላይ አድጎ 53 በመቶ መድረሱንም ጠቅሰዋል፡፡

እንደ አቶ መኩሪያ ገለፃ የሲሚንቶ ምርት ፍላጎትን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በሀገር ውስጥ ምርት መሸፈን የተቻለ ሲሆን ማርብል እና ግራናይትም 70 በመቶው በሀገር ውስጥ እየተመረተ እንደሆነ ጠቁመዋል።

የሌሎች የኮንስትራክሽን ግብዓቶችን አቅርቦት ለማሳደግም በዘላቂነት መስራት እንደሚደባ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ የኮንስትራክሽን ግብዓት ልማት አቅርቦት ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጠንክር መኩሪያ ተናግረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...