የሀገር ውስጥ የመድሃኒት ምርት የገበያ ድርሻ ወደ 41 በመቶ አደገ

Date:

በኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የመድሃኒት ምርት የገበያ ድርሻ ከ8 በመቶ ወደ 41 በመቶ ማደጉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ አስታወቁ።

ይህ ጭማሪ የመጣው የሀገር ውስጥ የመድሃኒት አምራቾች ምርቶች በግዥ ሂደት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው በመደረጉ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።

ምንም እንኳን እድገት ቢታይም፣ ለመድሃኒት ምርት የሚያገለግሉ አብዛኛዎቹ ጥሬ እቃዎች አሁንም ከውጭ የሚገቡ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቁመዋል። ይህንን ለመቀየር በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ እቃዎች ጥቅም ላይ መዋል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በበኩሉ፣ የካሳቫ ስታርች ምርት ለፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪዎች ያለውን አዋጭነት የሚያሳይ ጥናት ማድረጉን ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...