የትራምፕ የታሪፍ ውሳኔ አሜሪካውያን ሸማቾችን የሚጎዳ ነው ተባለ

Date:

ዶናልድ ትራምፕ፣ በውጭ ንግድ ላይ የጣሉት ቀረጥ የዓለም የንግድ ስርዓትን የሚያዛባ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ምሁሩ ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ ተናገሩ፡፡ የትራምፕ የታሪፍ ውሳኔ አሜሪካውያን ሸማቾችን የሚጎዳ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ እንደገለጹት፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ ጋር በሚነግዱ የዓለም ሀገራት ላይ በሙሉ ከ10 በመቶ ጀምሮ የጣሉት ቀረጥ የዓለምን የንግድ ስርዓት የሚያዛባ ነው፡፡ የፕሬዚዳንቱን ውሳኔ ተከትሎ ቀረጥ የተጣለባቸው ሀገራትም፣ የራሳቸውን ኢኮኖሚ ለመከላከል በአሜሪካ ላይ ቀረጥ እንዲጥሉ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡

የዓለም ሀገራት ለትራምፕ ውሳኔ የሚሰጡት ምላሽ መልሶ የሚጎዳው አሜሪካንን ነው ያሉት ምሁሩ፤ ይህ አይነቱ ሁኔታ የዓለምን የንግድ ሥርዓት እንደሚያዛባም አስታውቀዋል፡፡ የአሜሪካ ትልቁ አቅም ከሌሎች ጋር መነገድና ራሷን መቻሏ እንደነበር አንስተው፤ አሁን ላይ ግን እንደ ቻይና ያሉት ሀገራት ብሪክስን ይዘው በራሳቸው ገንዘብ ለመነገድ እየወሰኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ ደግሞ የሚጎዳው አሜሪካንን ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡

አሜሪካ የአረቢካ ቡናን ጨምሮ አንዳንድ ምርቶችን የግድ ከውጭ ማስገባት እንደሚኖርባት በመጠቆምም፣ የቀረጥ ውሳኔው ደግሞ አሜሪካዊያን ሸማቾችን የሚጎዳ ነው ብለዋል፡፡

የትራምፕ ሀሳብ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የአሜሪካን ኢኮኖሚ እናሳድጋለን ከሚል አመክንዮ የመጣ ነው ያሉት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ፤ ይህ ግን አሁን ላይ ጭምር የአሜሪካንን “ስቶክ ማርኬት” እየጎዳው እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

ጋዜጣ ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...