የትግራይ ትምህርት ቢሮ የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ተማሪዎችን ሊፈትን መሆኑን አስታወቀ

Date:



​የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ ባለመስማማት በራሱ አሠራር በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈተና አውጥቶ ተማሪዎችን ሊፈትን መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ ገለጹ።

​ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ ይህንን የገለጹት የ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መውጫ ፈተና አሰጣጥን አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።

እንደ ኃላፊው ማብራሪያ፣ በክልሉ በወረቀት ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበው ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ 15 ሺህ 349 ተፈታኝ ተማሪዎች ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ ፈተናቸውን እንዲወስዱ ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ የፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር ግን እስካሁን ድረስ የፈተና ወረቀቶችን ወደ ክልሉ አላከም።

ፈተናው በአውሮፕላን ተጓጉዞ በፌደራል ፖሊስ ጥበቃ የሚደረግለት በመሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት የፈተና ወረቀቱን ወደ ትግራይ ክልል ላለመላክ ምንም ዓይነት አሳማኝ ምክንያት የለም ሲሉ ኃላፊው ወቅሰዋል።

​የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ካቢኔ ለችግሩ እልባት እንዲሰጥበት ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ ቢልክም እስካሁን ይፋዊ ምላሽ አላገኘም።

ሐምሌ 1 ቀን ለሚጀምረው ፈተና ተማሪዎች በሰኔ 29 ቀን ወደየዩኒቨርሲቲዎቹ መግባት የነበረባቸው ቢሆንም፣ በትምህርት ሚኒስቴር ምክንያት በመቅረቱ ተማሪዎች ጉዟቸውን እንዲያቋርጡ ተደርጓል።

በትምህርት ሚኒስቴር የተላለፈው ይህ ውሳኔ የፖለቲካ ውሳኔና የጦርነቱ ቀጣይ አካል በመሆኑ ተቀባይነት የለውም ያሉት ዶክተር ኪሮስ፣ በትግራይ ክልል በኦንላይን (በኢንተርኔት) እና በወረቀት ሳይፈተኑ የቀሩ በአጠቃላይ 29 ሺህ 755 ተማሪዎችን ክልሉ የራሱን ፈተና በአጭር ጊዜ ውስጥ አዘጋጅቶ እንደሚፈትን አስታውቀዋል።

​በመጨረሻም የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የራሱን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ወስኖ ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚያስገባ የገለጹት ኃላፊው፣ ፈተናው የሚሰጥበት ትክክለኛ ጊዜ ወደፊት ይፋ እንደሚደረግና ተማሪዎች ይህንን አውቀው ዝግጅታቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...