ዶናልድ ትራምፕ በኻሚኒ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የኢራናውያንን ማልቀስ ማየታቸው «እንዳስገረማቸው» ገለጹ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአክሲዮስ (Axios) ሚዲያ ጋር ባደረጉት የስልክ ቃለ-መጠይቅ፤ በኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሚኒ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የሀገሪቱ ህዝብ ሲያለቅስ ማየታቸው በእጅጉ እንዳስገረማቸው አልጀዚራ ዘግቧል።

ትራምፕ በሰጡት አስተያየት «ህዝቡ በሙሉ የሚጠላው ይመስለኝ ነበር» በማለት ተገርመው ተናግረዋል።
 
ፕሬዚዳንቱ አክለውም የኢራን ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ በቀብሩ ላይ በአንድ ስፍራ ተሰብስበው ስለሚገኙ አሜሪካ «ሁሉንም በአንድ ጊዜ ማጥፋት» የምትችልበት የጦርነት አቅም እንዳላት ጠቁመው፤ ነገር ግን ይህንን ዛቻ ተግባራዊ ካደረጉት «ለመደራደር የሚተርፍ ሰው ስለማይኖር» ጥቃቱን ከመሰንዘር መቆጠባቸውን በግልጽ ተናግረዋል።
 
ትራምፕ ለሚዲያው እንደገለጹት፤ አሜሪካና ኢራን የኻሚኒ የቀብር ስነ-ስርዓት እስኪጠናቀቅ ድረስ በድርድርም ሆነ በወታደራዊ ግጭቶች ላይ ጊዜያዊ እረፍት ለመውሰድ ተስማምተዋል። በመሆኑም «በቀብር ስነ-ስርዓቱ ሂደት ወቅት የትኛውም ወገን በሌላው ላይ ጥይት አይተኩስም» ሲሉ አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጉምሩክ ኮሚሽን ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት 725.25 ቢሊዮን ብር...

ከ1.5 ሚሊዮን ዶላር የአፍሪካ ንፁህ ኢነርጂ ፈንድ አምስቱ አቅኚ የኢትዮጵያ ድርጅቶች ተመረጡ

በምስራቅ አፍሪካ የንፁህ ኢነርጂ አቅርቦትን በማሳደግ የስራ እድልን ለመፍጠርና...

ታላቅ የምስጋና እና የስጦታ መርሃ-ግብር ጥሪ!

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ባለፉት 5 ዓመታት ላበረከቱት ከፍተኛና ታላቅ...

የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ

ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን...