ዶናልድ ትራምፕ በኻሚኒ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የኢራናውያንን ማልቀስ ማየታቸው «እንዳስገረማቸው» ገለጹ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአክሲዮስ (Axios) ሚዲያ ጋር ባደረጉት የስልክ ቃለ-መጠይቅ፤ በኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሚኒ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የሀገሪቱ ህዝብ ሲያለቅስ ማየታቸው በእጅጉ እንዳስገረማቸው አልጀዚራ ዘግቧል።

ትራምፕ በሰጡት አስተያየት «ህዝቡ በሙሉ የሚጠላው ይመስለኝ ነበር» በማለት ተገርመው ተናግረዋል።
 
ፕሬዚዳንቱ አክለውም የኢራን ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ በቀብሩ ላይ በአንድ ስፍራ ተሰብስበው ስለሚገኙ አሜሪካ «ሁሉንም በአንድ ጊዜ ማጥፋት» የምትችልበት የጦርነት አቅም እንዳላት ጠቁመው፤ ነገር ግን ይህንን ዛቻ ተግባራዊ ካደረጉት «ለመደራደር የሚተርፍ ሰው ስለማይኖር» ጥቃቱን ከመሰንዘር መቆጠባቸውን በግልጽ ተናግረዋል።
 
ትራምፕ ለሚዲያው እንደገለጹት፤ አሜሪካና ኢራን የኻሚኒ የቀብር ስነ-ስርዓት እስኪጠናቀቅ ድረስ በድርድርም ሆነ በወታደራዊ ግጭቶች ላይ ጊዜያዊ እረፍት ለመውሰድ ተስማምተዋል። በመሆኑም «በቀብር ስነ-ስርዓቱ ሂደት ወቅት የትኛውም ወገን በሌላው ላይ ጥይት አይተኩስም» ሲሉ አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...