ታዋቂዎቹን ስታንዳርድ ቻርተርድ እና በርክሌይን ጨምሮ የውጭ ባንኮች ከአፍሪካ እየወጡ ነው፤ ለምን?

Date:

ታዋቂዎቹን የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ ባንኮች ስታንዳርድ ቻርተርድ እና በርክሌይን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ የውጭ ባንኮች ከአፍሪካ እየወጡ መሆናቸውን ጥናት አመላከተ።

ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ኒው ዮርክ ሰቨን የዓለም የንግድ ማዕከል ያደረገውና ከተመሰረተ 116 ዓመታትን ያስቆጠረው የሀገራትንና የኩባንያዎችን እዳና ብድር በመለካት ዓለም አቀፉ “ሙዲስ/Moody’s/” ኩባንያ አዲስ ባወጣው ሪፖርት ዓለም አቀፍ የውጭ ባንኮች ከሀገረ ደቡብ አፍሪካና ከአፍሪካ እየወጡ መሆናቸውን አመላክቷል።

በአህጉሪቱ የአገር ውስጥ ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማትና አዳዲስ ዲጂታል ተገዳዳሪዎች ዘርፉን በበላይነት መቆጣጠራቸው ለውጭ ባንኮች ከአፍሪካ መውጣት ዋነኛው መንስኤ መሆኑን የጥናቱ ሪፖርት ገልጿል።

በዚህም የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተዋናዮችና ሞባይል ባንኪንግንና ሌሎችንም ዲጊታል ባንኪንግ ዘዴዎች በመጠቀም በከፍተኛ ደረጃ ለሕብረተሰባቸው ብድርና ሌሎች የባንክ አገልግሎቶችን የሚያቀርቡ አዳዲስ የቴክኖ-ፋይናንስ ድርጅቶች ቀድመው በዘርፉ ጠንካራ መሠረት በመያዛቸው የተነሳ ዓለም አቀፍ የውጭ ባንኮች በደቡብ አፍሪካና በሌሎችም የአፍሪካ ክፍሎች የብድር አገልግሎቶችን በመስጠት ትርፋማ ለመሆን እየተቸገሩ መጥተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በአህጉሪቱ አሁንም ድረስ መሠረተ ልማት በበቂ ሁኔታ አለመስፋፋት፣ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ብሔራዊ የማንነት መለያ ሥርዓት አለመዘርጋትና መሰል መዋቅራዊ ተግዳሮቶች መኖራቸውና ይህም በዘርፉ ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማስመዝገብ ማነቆ መሆኑ ለውጭ ባንኮቹ ከአፍሪካ መውጣት በተጨማሪ መንስኤነት ቀርበዋል።

(አዲስ_ማለዳ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...