የነዳጅ ግብይት ሥርዓትና የመንግሥት የቁጥጥር እርምጃ

Date:

በዓለም አቀፍ ደረጃ በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ግጭት ሳቢያ የነዳጅ አቅርቦት መዛባትና የዋጋ ንረት እያጋጠመ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በኢትዮጵያም መንግሥት የዋጋ ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ መንግሥት ለነዳጅ አቅርቦት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ድጎማ እያደረገ ቢሆንም፤ ነዳጅን ከተቀመጠለት የዋጋ ተመን በላይ በመሸጥ ህገ-ወጥ ትርፍ ለማካበት የሚጥሩ አካላት መበራከታቸውን በጥናት ተረጋግጧል።

ይህንን ተከትሎም፣ ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈጸሙ የግል ነጋዴዎችንና የመንግሥት ተቋማትን ጨምሮ ተባባሪ የሆኑ አካላትን በቁጥጥር ስር የማዋል ሰፊ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ተጀምሯል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በዓለም ገበያ ካለው ከፍተኛ ጭማሪ አንጻር የተደረገው የዋጋ ማስተካከያ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይም የቁጠባ ግብይት ሥርዓት ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

በመሆኑም ሕዝቡ ይህንን ሕገ-ወጥ ንግድ በመከላከል ረገድ ከመንግሥት ጎን እንዲቆም ጥሪ ቀርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...