የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ህልፈት

Date:


የቀድሞው የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዲክ ቼኒ በ84 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ምክትል ፕሬዝዳንት ዲክ ቼኒ ከአውሮፓውያኑ 2001 እስከ 2009 የቀድሞ ሪፐብሊካን መሪ ጆርጅ ደብሊው ቡሽ ምክትል በመሆን አገልግለዋል፡፡

ህልፈታቸውን ተከትሎ የቀድሞው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ቡሽ፤ የቼኒ ህልፈት ለሀገር ትልቅ ኪሳራ፤ ለወዳጆቹ ደግሞ መሪር ሀዘን ነው ብለዋል፡፡

ቼኒ ሀገራቸውን የሚወዱ፣ለህዝብ የቆሙ፣ታታሪና እና የቅን ልብ ባለቤትም ነበሩ ሲሉ ቡሽ ገልፀዋቸዋል፡፡

ምክትል ፕሬዝዳንቱ ህይወታቸው ያለፈው ባደረባቸው ከልብ እና ደም ቧንቧ ህመም ጋር በተያያዘ መሆኑን ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል፡፡

ዲክ ቼኒ ከ1970 ማለትም ከፕሬዝዳንት ጄራልድ ፎርድ አመራር አንስቶ በተለያዩ የስራ ኃላፊነቶች በአሜሪካ ፖለቲካ ሀውስ ውስጥ ማገልገላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...