የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ  ሽሬ ገብተዋል

Date:

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቭን ሆሴ ማሲንጋ ዛሬ ጠዋት ሽሬ ከተማ ገብተዋል፡፡

የአምባሳደሩ ወደ የሽሬ ከተማ ጉብኝት ዓላማ፣ የአሜሪካ መንግስት ለተፈናቃዮች የሚያደርገው የሰብዓዊ ድጋፍ ያለበትን ሁኔታ ለመገምገምና የፕሪቶሪያውን የተኩስ አቁም ሙሉ በሙሉ  በሚተገብሩበት ሁኔታ ላይ በመምከር ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ነው ተብሏል፡፡

አምባሳደሩ ሙሉ ቀን በሚወስደው ጉብኝታቸው፣ ከአካባቢው መሪዎች ጋር በመገናኘት በፖለቲካ አካታችነትና በሰላም ዙሪያ እንደሚመክሩም በአሜሪካ ኤምባሲ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ባሰፈሩት መረጃ ጠቁመዋል፡፡

ይህን ተከትሎም  በርካታ የህወሓት ጄኔራሎች ትናንት  ሽሬ ገብተው ማደራቸው ታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...