የአዲስ አበባ ጤና ባለሙያዎች የትርፍ ሰዓት ክፍያን ጨምሮ አዲስ የጥቅማጥቅም ፓኬጅ ተፈቀደ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች የትርፍ ሰዓት ክፍያን ጨምሮ አዲስና አጠቃላይ የጥቅማጥቅም ፓኬጅ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ መተላለፉን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ እንደገለጸው፣ የከተማዋ ካቢኔ የጤና ባለሙያዎችን ጥቅማጥቅም ለማሻሻል በቀረበለት ጥያቄ ላይ ተወያይቶ አራት አንኳር ውሳኔዎችን ማሳለፉን አስታውሷል።

እነዚህ ውሳኔዎች የጤና ባለሙያዎችን የስራ ሁኔታ ለማሻሻል እና የኑሮ ጫናቸውን ለማቃለል ታስበው የተዘጋጁ መሆናቸው ተጠቁሟል።

ቢሮው በሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በጻፈው ሰርኩላር ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው፣ ከተፈቀዱት አዳዲስ ጥቅማጥቅሞች መካከል የጤና ባለሙያዎች የትርፍ ሰዓት ክፍያ አፈፃፀማቸው በአገልግሎት ስታንዳርዱ መሰረት እንዲፈፀም የሚለው ይገኝበታል።

በተጨማሪም በዚህ የጥቅማጥቅም ፓኬጅ ደብዳቤ ላይ እንደሰፈረው፣ የጤና ባለሙያዎች የትዳር አጋርና እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ልጆቻቸው ሙሉ በሙሉ ነጻ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ተፈቅዷል። በቀዳማዊ ልጅነት የልማት ፕሮጀክት የተቀጠሩ የቤት ለቤት የምክር አገልግሎት ሰጪዎችም፣ አሰራሩን የጠበቀ ቋሚ የስራ ምድብ እንዲሰጣቸው ውሳኔ ተላልፏል።

ይህ አዲስ ፓኬጅ ከ2018 በጀት ዓመት ( ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም.) ጀምሮ ተግባራዊ ሲሆን፣ የጤና ባለሙያዎችን የሞራልና የስራ ተነሳሽነት ከፍ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...