“የአፍሪካን ብዝሃነት ለማሳየት ከሥነ-ጥበብ፣ ፋሽን እና ሙዚቃ ውጪ የተሻለ መንገድ የለም”

Date:



የብራንድ አፍሪካ መሥራች እና ሰብሳቢ ቴቤ ኤካላፌንግ አፍሪካውያን በፈጠራ መስክ በዓለም አቀፍ ደረጃ ልቀው እየተገኙ ነው ይላሉ።

አዲስ አበባ ተካሂዶ በነበረው የብራንድ አፍሪካ የሽልማት ዝግጅት ላይ ሲናገሩ በፈጠራ ዘርፍ የሚወጡ ምርቶች እና አገልግሎቶች አህጉሪቱን የበለጠ ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።

“እንደ እኔ አመላካከት በዓለም አቀፍ ደረጃ አፍሪካዊነትን ለመግለፅ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ነጻነት እድል ይሰጡናል።”

በሙዚቃ ዘርፍ ጉምቱ የሚባሉትን ከደቡብ አፍሪካ ሚሬም ማኬባና ሂው ማሴኬላ፣ ናይጄሪያዊው ፌላ ኩቲን፤ በፋሽን ዘርፍ የቀድሞዋ ዓለም አቀፍ ሞዴል ኢትዮጵያዊቷ አና ጌታነህ አፍሪካን በማስተዋወቅ ረገድ የተጫወቱትን ጉልህ ሚና አንስተዋል።

“ለምንድነው የእኛ የተሻለ እና የሚያምር ሆኖ ሳለ ኸርምስ፣ ሉዊ ቭታን፣ ዶልቼ እና ባሌንሲያጋን የምንለብሰው። አዚህ ኢትዮጵያ ስንመጣ ኢትዮጵያዊያን ራሳቸውን መስለው ሲታዩ ደስ ይላል። ስታይል፣ ፋሽን፣ ሐይማኖታቸው እና ፊደላቸው በጣም የተለየ ነው” ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...