የአፍሪካ ህብረት አዲሱ የአሜሪካ ታሪፎች የአስርተ አመታት የንግድ ትብብርን አደጋ ላይ ይጥላሉ አለ

Date:

የአፍሪካ ህብረት እንዳስታወቀው በአህጉሪቱ ላይ በአሜሪካ የተጣሉ አዲሶቹ ታሪፎች የአስርተ አመታት የዘለቀውን “በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ የንግድ እና የትብብር” ግንኙነትን አደጋ ላይ እንደሚጥሉ አስጠንቅቋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሃሙድ አሊ የሱፍ የአሜሪካ መንግስት በወሰደው የጣሪፍ ጭማሪ ላይ ያላቸውን ጥልቅ ስጋት በመግለጽ ይህንንም ውሳኔ እንደገና እንዲያጤነው አሳስበዋል።

አሜሪካ የረዥም ጊዜ እሴቶች እና በጋራ ምኞቶች ላይ የተመሰረተውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ከማጠናከር ይልቅ ማዳከም ተገቢ አይደለም ማለታቸው ተነግሯል።

በተለይም እንደ ትልቅ የጨርቃ ጨርቅ ላኪ የሆነችው ሌሶቶ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ የተጣለባት ሲሆን ደቡብ አፍሪካ፣ ማዳጋስካር እና ቦትስዋና ደግሞ ከ 30 በመቶ በላይ በሆነ የታሪፍ ጭማሪ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...