የኢራን አብዮታዊ ዘብ ቃል አቀባይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መገደላቸውን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ቃል አቀባይ እና ምክትል ሕዝብ ግንኙነት አሊ ሞሃመድ ናኢኒ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃቶች መገደላቸውን የአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን አስታውቋል።
አሊ ሞሐመድ ናኢኒ የአብዮታዊ ዘቡን ለአራት አስርታት ያገለገሉ ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ደግሞ ቃል አቀባይ በመሆን ሰርተዋል ሲል ፋርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21 2018 ዓ.ም. ኢራን ላይ ጦርነት ከከፈቱበት ዕለት አንስቶ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ በርካታ አመራሮች ተገድለዋል።
የቀድሞው ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ጦርነቱ በጀመረ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ የተገደሉ ሲሆን ሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ አመራሮችም የአሜሪካ እና የእስራኤል ጥቃት ዒላማ ሆነዋል።
