የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

Date:

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው ላይ ለተፈጸመው ግድያ “የበቀል እርምጃ” መወሰድ እንዳለበት አሳሰቡ።

የቀድሞው ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ኻሜኒ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት የመጀመሪያው ቀን መገደላቸው ይታወሳል።

የአባታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ለተገኙ ሰዎች ምስጋና ያቀረቡት ሞጅታባ ኻሜኒ “ንጹህ ደምን ለመበቀል ቃል እንገባለን” ብለዋል።

“ወንጀለኛ እና የተዋረዱ ገዳዮች በከፈቷቸው ሁለት ጦርነቶች ለተገደሉ ሰማዕታትም የበቀል እርምጃ ይኖራል” ሲሉም አክለዋል።

አዲሱ ጠቅላይ መሪ “ይህ በቀል የአገራችን ፍላጎት ነው። እንደምንፈጽመው ጥርጥር የለም” ብለዋል።

የአባታቸው አያቶላህ ዓሊ ኻሜኒን ግድያ ተከትሎ አዲሱ ጠቅላይ መሪ ኃላፊነቱን ተረክበዋል።

እስካሁን ድረስ በይፋ ያልታዩ ሲሆን በቪድዮ እና በድምጽም መልዕክት አላስተላለፉም።

በአባታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ያልተገኙት ሞጅታባ ኻሜኒ መልዕክት የሚያደርሱት በጽሑፍ ብቻ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...

የአርሲ አሰኮ ተፈናቃዮች በርዳታ አቅርቦቶች መቋረጥ መቸገራቸውን ገለጹ

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ግንቦት...