የኢትዮጵያ ንግድ ፖሊሲ ከሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታውን ባገናዘበ መልኩ ለመስራት ያስችላል

Date:

የሀገራችን ንግድ ለ117 ዓመታት ያለፖሊሲ ሲሰራበት ቆይቶ አሁን ተዘጋጅቶች ለመጨረሻ አስተያየት የቀረበው የኢትዮጰያ ንግድ ፖሊሲ የሀገራችንን ሁኔታ ከውጪው ዓለም ጋር በማስገንዘብ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ፖሊሲው የተዘጋጀው በምሁራን ተሳትፎ የተካሄደ ጥናት እና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ ጸድቆ ወደተግባር ሲገባ ለንግዱ ማህበረሰብ በጣም ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡
ሌሎች ሀገራት የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት በተመለከተ ለሚጠይቁት ጥያቄ መልስ የሚሰጥ እንዲሁም የኢትዮጵያን የንግድ መልከዓ ምድር የሚያሳይ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለምታካሂደው የዓለም ንግድ ድርጀት የአባልነት ድርድር እና ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ ሀገራዊ ጠቅምን ያስከበረ ፋይዳ የኖረዋል በማለት አስገዝበዋል፡፡

ረቂቅ የንግድ ፖሊሲው በዛሬው እለት በተካሄደው ከባለድርሻ አካላት የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ በተገኙ ገንቢ አስተያየቶች ዳብሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሚመለከተው አካል ይቀርባልም ብለዋል፡፡

ምንጭ ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒሰቴር

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...