የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የሰነድ ማስረከቢያ ጊዜን አራዘመ

Date:

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በህዝብ የተያዙ ኩባንያዎች አስፈላጊ ሰነዶችን እና መረጃዎችን እንዲያቀርቡ የተሰጠውን ቀነ-ገደብ ለአንድ ወር ማራዘሙን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ቀደም ሲል ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ኩባንያዎቹ እስከ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሰነዶችንና መረጃዎችን እንዲያቀርቡ አሳስቦ ነበር። ነገር ግን፣ ከኩባንያዎቹ የቀረቡትን ጥያቄዎች እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለመቀበል እንዲቻል የጊዜ ገደቡ እስከ ሚያዚያ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ተራዝሟል።

ይህ ማራዘሚያ አስፈላጊውን መረጃ እስካሁን ላላቀረቡ ኩባንያናት የመጨረሻ እድል እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ባለስልጣኑ ኩባንያናቱ የተራዘመውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም አስፈላጊ ሰነዶችንና መረጃዎችን እንዲያቀርቡ አሳስቧል።

ማራዘሚያው ከ50 በላይ የአክሲዮን ባለቤቶች ያሏቸው እና በአሁኑ ወቅት አክሲዮኖችን ለህዝብ ሽያጭ በማቅረብ ላይ ያሉ ኩባንያዎችን ይመለከታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...