የካሜሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ለኢትዮ ቴሌኮም እና ካምቴል ጥምረት መንግሥታቸው ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋገጡ

Date:

የካሜሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆሴፍ ዲዮን ንጉቴ (ዶ/ር) ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩን እና የካምቴል ዋና ዳይሬክተር ጁዲት ያህ ሳንዴይን አነጋግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዲጂታል ሽግግር ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ በመሆኑ የአፍሪካ ኦፕሬተሮች ትብብር ወሳኝነት ገልጸው የኢትዮጵያ የዲጂታል ተሞክሮ በሀገራቸው እንዲተገበር ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው፤ ኢትዮ ቴሌኮም በመሰረተ ልማት፣ አገልግሎት ተደራሽነት፣ በዋጋ ተመጣጣኝነት እና በፋይናንስ አካታችነት ያካበተውን ልምድ በማካፈል የካሜሩንን የዲጂታል ራዕይ እንደሚያግዙ ገልጸዋል።

ይህ የዲጂታል መሰረተ ልማት ማስፋፋት ኢኮኖሚን ከማነቃቃቱም ባለፈ፣ ትብብሩ ለአፍሪካ ኦፕሬተሮች አርአያ እንደሚሆን አክለው ተናግረዋል።

የካምቴል ዋና ዳይሬክተር ጁዲት ያህ ሳንዴይ፣ የኢትዮ ቴሌኮምን ሀገራዊ የዲጂታላይዜሽን ስኬት በአካል መመልከታቸውን አስታውሰው፣ ይህንኑ ልምድ በሀገራቸው እንደሚተገብሩ አረጋግጠዋል።

ልዑካን ቡድኑ ከካሜሩን የፖስታ እና ቴሌኮሙኒኬሽን እንዲሁም ከሠራተኛ እና ማህበራዊ ዋስትና ሚኒስትሮች ጋርም ተወያይቷል።

Ethiotelecom

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...

ሕወሓት ድብረጺዮንን የክልሉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

የክልሉ ፕሬዚዳንት ተደርገው የተመረጡት  ድብርጺዮን ገ/ ሚካዔል (ዶ/ር)  ቃለ...