የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንዲኖራቸው የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ለምክር ቤት ተላለፈ

Date:

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ፀደቀ።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በረቂቅ አዋጁ ላይ ባደረገው ውይይት፣ ይህ አዲስ አሠራር የዜጎችን የመሬት ይዞታ የማግኘትና የመጠቀም መብት በማያጣብብ መልኩ ለውጭ ዜጎች ህጋዊ መሠረት መዘርጋቱ ለሀገሪቱ በርካታ ጥቅሞች እንዳሉት አጽንኦት ሰጥቷል።

ከእነዚህም ጥቅሞች መካከል የውጭ ካፒታል ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ ማበረታታት፣ የቤት ልማትና ተደራሽነትን ማነቃቃት፣ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦትን ሚዛናዊ ማድረግ እንዲሁም ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይጠቀሳሉ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ይህን ረቂቅ አዋጅ አፅድቆ ወደ ተግባር ሲገባ የውጭ ኢንቨስትመንትን በማሳደግና የሪል ስቴት ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...