የዱባይ የቅንጦት ሆቴል በኢራን ሚሳኤል ጋየ

Date:

​በዱባይ የሚገኘው ታዋቂው ‘ፌርሞንት ዘ ፓልም’ የቅንጦት ሆቴል በደረሰበት የእሳት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት አስተናገደ።

አደጋው የተከሰተው ኢራን በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላይ በሰነዘረችው የሚሳኤል ጥቃት ወቅት የተተኮሱ ሚሳኤሎች ተመተው ሲወድቁ ባረፉ ፍንጣሪዎች መሆኑ ተገልጿል።

​አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ “ኤፒክ ራዝ” እና “ላየንስ ሮር” የተሰኙ ጥቃቶችን መሰንዘራቸውን ተከትሎ፣ ኢራን በአጸፋው በዱባይ፣ ባህሬን እና ኳታር በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ጥቃት ፈጽማለች።

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር አዳዲስ የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል።

​በአሁኑ ወቅት በዱባይ አየር ማረፊያዎች ተዘግተው ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን፣ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የት እንዳሉ አለመታወቁ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...