የዶቸ ቬለ ዘጋቢዎችን እንዳይዘግቡ ታገዱ

Date:


የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለዶቸ ቬለ የሚዘግቡ ጋዜጠኞች ዘገባ እንዳይሰሩ አገዱ።

ዶቸ ቬለ ከ1980ዎቹ ጀምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በሚገኙ ዘጋቢዎች አማካይነት የኢትዮጵያን ፖለ,ቲካዊ፣ ምጣኔ ሐብታዊና ማሕበራዊ ጉዳዮችን እና የአፍሪቃ ሕብረትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ አካባቢያዊ፣ አሐጉራዊና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ተቋማትና ማሕበራትን እንቅስቃሴና ክንዋኔዎችን ሲዘግብ ቆይቷል።


ዓለምአቀፉ ማሰራጪያ ጣቢያ ከ 2010 ጀምሮ የወኪሎቹን ቁጥር በማሳደግ መቀሌ፣ ባሕርዳር፣ ደሴ፣ አዲስ አበባ፣ ሐዋሳ፣ ድሬዳዋና አሶሳ በሚገኙ 9 ወኪሎቹ አማካይነት መረጃዎችን በማሰባሰብ ገለልተኛ፣ ሚዛናዊ ዘገባዎችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያሰራጫል።

ይሁንና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዛሬ በፃፈዉ ደብዳቤዉ ዶቼ ቬለና ወኪሎቹን የኢትዮጵያን ሕግና ደንብ ጥሰዋል፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን አያከብሩም በማለት ወቅሷል።


ከዛሬ ጀምሮ ኢትዮጵያ የሚገኙ የዶቸ ቬለ ዘጋቢዎችን የሥራ ፈቃድ ለጊዜዉ ማገዱን አስታዉቋል። ባለሥልጣኑ «ጊዚያዊ» ያለዉ እግዳ ሥለሚቆይበት ጊዜ የገለፀዉ ነገር የለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...