የዶይቼ ቬለ የአማርኛው 60ኛ ዓመት

Date:

የዶይቼ ቬለ የአማርኛው ክፍል የመንግሥታት መለዋወጥ ሳይበግረው መረጃን ለአድማጮቹ እያደረሰ የዘለቀ የራዲዮ ጣቢያ መሆኑን የዶቼ ቬለ የአፍሪካ ክፍል ሀላፊ ክላውስ ሽቴከር ገለፁ። 


ሃላፊው የጣቢያውን 60ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በተደረገ ልዩ የክብረ በዓል ድግስ ላይ ተገኝተው እንደገለፁት፤ የዶይቼ ቬለ የአማርኛው ክፍል የመንግሥታት መለዋወጥ፣ የፀጥታ ችግር እና ሌሎች ፈተናዎች ሳይበግሩት መረጃዎችን ለኢትዮጵያውን አድማጮቹ እያደረሰ ዛሬም አለ። ለዚህም የጣቢያው ተግባር እውቅና እና ከበሬታ እንደሚሰጡ ሀላፊው አመልክተዋል። ለወደፊቱም ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋቸውን ገልጸዋል።


በራዲዮ የተጀመረው አገልግሎት በጊዜ ሂደት ከተፈጠሩ የቴክኖሎጂ ለውጦች ጋር ራሱን እያስማማ ዛሬ በድረ-ገጽ እና እንደ ፌስቡክ፣ ዩቲዩብ፣ ቴሌግራም በመሳሰሉ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ለተከታታዮች እያቀረበ ይገኛል ያሉት ሀላፊው፤ በዚህ የቴክኖሎጂ ለውጥ ከተደረገው ሽግግር ጋር ራሱን በማስማማቱ የጣቢያውን ኤዲቶሪያል አመስግነዋል።


የዶይቼ ቬለ የአማርኛ አገልግሎት ለኢትዮጵያና ለአካባቢዉ ሃገራት ማሰራጨት የጀመረዉ መጋቢት 6 ቀን 1957 ነበር። ጣቢያዉ የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ እና የዓለምን ዐበይት ጉዳዮች በዜና እና በትንታኔ እያቀረበ ስድስት አስርት ዓመታትን ከአድማጮቹ ጋር ዘልቋል።


ዶይቼ ቬለ የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት የተጀመረበትን 60ኛ ዓመት አስመልክቶ በተዘጋጀው ልዩ ድግስ የዶይቼ ቬለ ኃላፊዎች፣ የአማርኛ ቋንቋ ክፍል የወቅቱ እና የቀድሞ ጋዜጠኞች እንዲሁም ዶቼ ቬለ የሚያሰራጭባቸው የልዩ ልዩ ቋንቋ ክፍል ባልደረቦችም ተገኝተው የበዓሉ ተካፋዮች ሆነዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...