የገንዘብ ሚኒስቴር አዲስ የገቢ ግብር ረቂቅ ደንብ ማዘጋጀቱን አስታወቀ

Date:

አዲሱ መመሪያ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017ን ለማስፈጸም ያለመ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ነዋሪ ሆነው ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ምንጮች በዲጂታል አማራጮች ገቢ የሚያገኙ ግለሰቦችን በሙሉ የሚመለከት ነው።

ረቂቅ ደንቡ በተለይ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች በጥሬ ገንዘብም ሆነ በዓይነት የሚያገኙትን ገቢ በትክክል የሚገልጽ የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ እንደሚኖርባቸው ይደነግጋል።

ከዚህም በተጨማሪ ለፈጣሪዎቹ ክፍያ የሚያመቻቹ ኩባንያዎች ስለ ተከፋዮቹ ማንነትና የክፍያ መጠን በየሩብ ዓመቱ ለታክስ ባለሥልጣኑ ሪፖርት እንዲያደርጉ ይጠበቅባቸዋል።

ሚኒስቴሩ ማንኛውም ፍላጎት ያለው አካል በረቂቁ ላይ ያለውን አስተያየት እስከ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በጽሑፍ ወይም በኢሜል እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርቧል።

ይህ እርምጃ በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ከነባሩ የግብር ሥርዓት ጋር ለማስተሳሰር የተወሰደ ትልቅ እርምጃ እንደሆነ ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...