የጭነት መኪና ተገልብጦ የ11 ሰዎች ህይወት አለፈ

Date:

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ሸነን ዱጎ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 11 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የዞኑ ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

በተለምዶ አይሱዙ የተሰኘው የደረቅ ጭነት መኩና 42 ሰዎችን ከተለያዩ ሸቀጦች ጋር ጭኖ ከዋልዳያ ከተማ ወደ መሰላ ወረዳ በመጓዝ ላይ ሳለ በትላንትናው ዕለት ምሸት 2:30 ላይ ነው አደጋው የደረሰው።

መኪናው 42 ሰዎዎችን ከተለያዩ እቃዎች ጋር አብሮ ጭኖ የነበረ ሲሆን መስመሩን በመሳት ከ50 እስከ 70 ሜትር በሚርቅ ገደል ውስጥ የገባ ሲሆን በዚህም የ 11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ነው የተገለጸው።

በአደጋው በተጨማሪም በ28 ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን በሂርና የመጀመሪያ ሆስፒታል እንዲሁም በጭሮ አጠቃላይ ሆስፒታል ክትትል እየተደረገላቸው ነው።

የአደጋው ምክንያትም የጥንቃቄ ጉድለትና ከአቅም በላይ መጫን መሆኑን የወረዳው የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ኢንስፔክተር ረቢራ አየለ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...