የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአንድ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠቱን አስታውቋል።
ቦርዱ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዓ.ም. በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ሰጥቷል።
የምስክር ወረቀቱ የተሰጠው ውድብ ወልዶ ትግሪይ ለተባለው የፖለቲካ ፓርቲ ነው። ሰነዱ ትላንት ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ተሰጥቷል።
ይህ በህጋዊ ሰነድ መረጋገጡ ፓርቲው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የመሳተፍ መብቱንና ሥልጣኑን ያጎናጽፈዋል።
