የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ጀመረ

Date:

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ መሆኑን አስታውቋል።

ተፈታኞች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ምዝገባቸውን ማጠናቀቅ እንዳለባቸው ያሳሰበው አገልግሎቱ፣ ለምዝገባው ሂደት አስፈላጊ የሆኑ መመሪያዎችንም ይፋ አድርጓል።

በመመሪያው መሠረት መደበኛ ተፈታኞች በትምህርት ቤቶቻቸው አማካኝነት ምዝገባቸውን የሚያከናውኑ ሲሆን፣ ቀደም ሲል ተፈትነው ውጤት ለማሻሻል ወይም በግላቸው ድጋሚ ለመፈተን የሚፈልጉ ተማሪዎች ደግሞ በራስ-አገዝ (Self-service) የኦንላይን ዘዴ መመዝገብ ይኖርባቸዋል።

የግል ተፈታኞች ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀውን https://register.eaes.et የተሰኘ ድረ-ገጽ በመጠቀም ምዝገባቸውን እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀርቧል።

ማንኛውም ተፈታኝ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ካልተመዘገበ በስተቀር ለፈተና መቀመጥ የማይችል መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በጥብቅ አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ንባብ ለህይወት!” ታላቅ የንባብ ሳምንት እና የመጻሕፍት አውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የንባብ ለህይወት...

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...