ዩናይትድ ኪንግደም የ2035 የሴቶች የአለም ዋንጫን ለማዘጋጀት ጥያቄ አቀረበች

Date:

በአለም እግር ኳስ ላይ ከፍተኛ አስተዋጾ ያደረጋሉ ከሚባሉ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ዩናይትድ ኪንግደም የ2035 የሴቶች የአለም ዋንጫን ለማዘጋጀት ለፊፋ ጥያቄ እንዳቀረበች ታውቋል፡፡

የእንግሊዝ፣ የዌልስ፣ የስኮትላንድ እና የሰሜን አየርላንድ የእግር ኳስ ማህበር ውድድሩን በጋራ ለማስተናገድ ፍላጎት እንዳለቸው መግለጫ አውጥዋል፡፡

ይህም የሚሳካ ከሆነ እንግሊዝ የሴቶች የአለም ዋንጫን ስታሰናዳ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሆናል፡፡

እ.ኤ.አ. 2035 ላይ ሊደረግ ለታሰበው የሴቶች የአለም ዋንጫ ጥያቄ ያቀረቡ ሀገራትን ለመመልከት በፊፋ ምክር ቤት አዘጋጅነት ስብሰባ እንደተቀመጡ ተነግሯል፡፡

አለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ (ፊፋ) እንዳለው ከዩኤፍ እና ከካፍ የተገኙ አባል ሀገራት ለዚህ ውድድር ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል፡፡

በዚህም ፊፋ በ2031 እና 2035 የሴቶች የአለም ዋንጫን የሚያዘጋጁ ሀገራትን በ2026 ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ዩናይትድ ኪንግደም ጥያቄ ማቅረቧን ተከትሎ የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪየር ስታርመር እንዳሉት “የፊፋ የሴቶች የዓለም ዋንጫ 2035 በሀገራችን ለማዘጋጀት ጥያቄ ማቅረባችን በስፖርት ታሪካችን ውስጥ ሌላ ትልቅ እንድምታ ይኖረዋል፣ እድገትን የሚያመጣ እና ዘላቂ ትሩፋት የሚይዝ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ዩናይትድ ኪንግደም በ2040 ልታስተናግድ ከምትችላቸው 70 ዋና ዋና የስፖርት ዝግጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የሴቶች የአለም ዋንጫ መታወቁን በመንግስት የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግለት ይጠበቃል ተብሏል፡፡(ሀገሬ ቴቪ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...