“ ደጋፊዎች በነቂስ ወጥተው እንደሚደግፉን ተስፋ አደርጋለሁ “

Date:

የኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ቤንጃሚን ዚመር ዛሬ ደጋፊው በነቂስ ወጥቶ እንዲያበረታታቸው ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር ወሳኝ ጨዋታውን ያደርጋል።

ከጨዋታው በፊት አስተያየታቸውን የሰጡት አሰልጣኝ ዚመር “ ደጋፊው በነቂስ ወጥቶ እንደሚደግፈን ተስፋ አደርጋለሁ “ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ቡድኑ ጥሩ ዝግጅት ማድረጉን ያነሱት አሰልጣኙ ለዩጋንዳ ክብር እንደሚሰጡ ገልፀው እነሱ በእግርኳሱ ጥሩ እየሰሩ ያሉ ናቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ቡድኑ ተረጋግቶ እንዲፎካከር ሰርተናል “ ያሉት አሰልጣኙ “ የተቻላቸውን ጥረት በማድረግ ለሀገራቸው በፍቅር እንዲጫወቱ አሳስበናል ብለዋል።

የቡድኑ አምበል ቢኒያም አብረሀ በበኩሉ “ ከዚህ በፊት እንዳደረጋችሁት ዛሬም ድጋፋችሁን ስጡን እንጠብቃችኋለን “ ሲል ለደጋፊው መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethsport    

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...