ባንኩ በዳሸን ዕድል ጨዋታ አሸናፊ ለሆነ ወጣት የቢዋይዲ ሲግል መኪና አበርክቷል።
የባንኩ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ላለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ መርኃ ግብሮች ሲከበር ቆይቷል።
የአከባበር ሥነ ስርዓቱ ማጠቃለያ ፕሮግራም በትናንትናው ዕለት በሸራተን አዲስ ተካሂዷል።
በመርኃግበሩ ላይ የብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የፋይናንስ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች፣ የባንኩ ደንበኞች ተገኝተዋል።
የባንኩን ስያሜ ከማውጣት ጀምሮ የባንኩ ምስረታ ዕውን እንዲሆን ከፍተኛ ዕገዛ ላደረጉት ለሼክ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን የዕውቅና እና የማስታወሻ ሽልማት ተበርክቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለዳሽን ባንክ 11 ባለራዕይ መስራቾች፣ ለቀድሞ የስራ አመራር ቦርድ ኃላፊዎችና ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች፣ አጋር ተቋማት፣ የረዥም ዓመት ደንበኞች እንዲሁም ከዳሸን ባንክ ምስረታ አንስቶ ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ላገለገሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ዕውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል፡፡
ዳሽን ባንክ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለዲቦራ ፋውንዴሽን የ30 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በሌላ በኩል በዳሽን ሱፐር አፕ በቀረበውና እስከ 30 ሚሊዮን ብር የሚደርሱ ሽልማቶች በቀረቡበት የዳሽን ዕድል ጨዋታ የዘመናዊ ቢዋይዲ ሲግል የኤሌክትሪክ መኪና አሸናፊ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡
ሸገር 102.1
