ዳሸን ባንክ 30ኛ የምስረታ ዓመት በዓሉ ማጠቃለያ ላይ ለዲቦራ ፋውንዴሽን 30 ሚሊዮን ብር  ሰጠ

Date:

ባንኩ  በዳሸን ዕድል ጨዋታ አሸናፊ ለሆነ ወጣት የቢዋይዲ ሲግል መኪና አበርክቷል።

የባንኩ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን  ላለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ መርኃ ግብሮች ሲከበር ቆይቷል።

የአከባበር ሥነ ስርዓቱ ማጠቃለያ ፕሮግራም በትናንትናው ዕለት በሸራተን አዲስ ተካሂዷል።

በመርኃግበሩ ላይ የብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የፋይናንስ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች፣ የባንኩ ደንበኞች ተገኝተዋል።

የባንኩን ስያሜ ከማውጣት ጀምሮ የባንኩ ምስረታ ዕውን እንዲሆን ከፍተኛ ዕገዛ ላደረጉት ለሼክ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን የዕውቅና እና የማስታወሻ ሽልማት ተበርክቷል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ለዳሽን ባንክ 11 ባለራዕይ መስራቾች፣ ለቀድሞ የስራ አመራር ቦርድ ኃላፊዎችና ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች፣ አጋር ተቋማት፣ የረዥም ዓመት ደንበኞች እንዲሁም ከዳሸን ባንክ ምስረታ አንስቶ ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ላገለገሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ዕውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል፡፡

ዳሽን ባንክ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለዲቦራ ፋውንዴሽን የ30 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

በሌላ በኩል በዳሽን ሱፐር አፕ በቀረበውና እስከ 30 ሚሊዮን ብር የሚደርሱ ሽልማቶች በቀረቡበት የዳሽን ዕድል ጨዋታ የዘመናዊ ቢዋይዲ ሲግል የኤሌክትሪክ መኪና አሸናፊ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...