ዳንጎቴ ግሩፕ ወደ ወርቅና ሪል እስቴት ለመግባት አቅዷል

Date:

ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ኢንቨስትመንቶቹን ከሲሚንቶና ማዳበሪያ ባሻገር በሌሎች ዘርፎችም  ለማስፋፋት በዝግጅት ላይ ሲሆን፤ ወደ ወርቅ ማውጣትና የሪል እስቴት ዘርፉ  ለመግባት ማቀዱ ተሰምቷል፡፡

የዳንጎቴ ግሩፕ ሊቀመንበር አሊኮ ዳንጎቴ፣ ከሰሞኑ የ2.5 ቢሊዮን ዶላር የማዳበሪያ ማምረቻ ፕሮጀክት ስምምነት በተፈራረሙበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ “የወርቅ ማዕድን ዘርፍ ላይ የመሰማራት  እድሎችን እየተመለከትን ነው፣ እነዚህ ለኛ አዳዲስ ስራዎች ናቸው፣ ነገር ግን እንደ ስራ ፈጣሪ ኩባንያ እያንዳንዱን ኢንቬስትመንት እንፈልጋለን። ወደ ሪል እስቴትና  አፓርታማ ግንባታዎችም ልንገባ  እንችላለን” ብለዋል።

በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ኢንዱስትሪ ውስጥ ጠንካራ መሰረት ያለው ዳንጎቴ ግሩፕ፤ አሁን ደግሞ ወደ ሪል እስቴትና ወርቅ ማውጣት ዘርፍ ለመግባት ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...