ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ሩሲያ በኢትዮጵያ ኢንቨስት የምታደርግባቸውን ዘርፎች እንድታሰፋ ጥሪ አቀረቡ

Date:



የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንታዊ ሥራ አስፈፃሚ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ማክሲም ኦሬሽኪን እና ከሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭን ጋር ተገናኝተው በስትራቴጂካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

“ሩሲያ በተለያዩ የትብብር ዘርፎች ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆት አለን፡፡ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና በማዕድን ልማት እንዲሁም በማዳበሪያ ምርት፣ በብረታ ብረት ኢንዱስትሪ እና የኒውክሌር እና ታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በኃይል መሠረተ ልማት፤ ለሩሲያ ኢንቨስትመንት እና የጋራ ትብብር ጥሪ እናቀርባለን” ብለዋል፡፡  

▫️ እነዚህ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች በዘላቂ ልማት፣ በቀጣናዊ ደህንነት እና በጋራ ብልጽግና ላይ በማተኮር የኢትዮጵያ-ሩሲያ አጋርነትን ወደ አዲስ የስትራቴጂካዊ ትብብር ደረጃ ለማሳደግ ማሳያ ናቸው ሲል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማህበራዊ ገጹ አስታውቋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...