የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንታዊ ሥራ አስፈፃሚ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ማክሲም ኦሬሽኪን እና ከሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭን ጋር ተገናኝተው በስትራቴጂካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
“ሩሲያ በተለያዩ የትብብር ዘርፎች ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆት አለን፡፡ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና በማዕድን ልማት እንዲሁም በማዳበሪያ ምርት፣ በብረታ ብረት ኢንዱስትሪ እና የኒውክሌር እና ታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በኃይል መሠረተ ልማት፤ ለሩሲያ ኢንቨስትመንት እና የጋራ ትብብር ጥሪ እናቀርባለን” ብለዋል፡፡
▫️ እነዚህ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች በዘላቂ ልማት፣ በቀጣናዊ ደህንነት እና በጋራ ብልጽግና ላይ በማተኮር የኢትዮጵያ-ሩሲያ አጋርነትን ወደ አዲስ የስትራቴጂካዊ ትብብር ደረጃ ለማሳደግ ማሳያ ናቸው ሲል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማህበራዊ ገጹ አስታውቋል።
