ግብፅ ለኤርትራ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች

Date:

የሕክምና ቁሳቁስ የያዘ የግብፅ አውሮፕላን ባሳለፍነው ዓርብ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም. አስመራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መደረሱን የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ለኤርትራ የመድሃኒት አስተዳደር የተበረከተው ይህ እርዳታ፣ የዓይን ህክም እና የኩላሊት እጥበት መስሪያ ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው። እርዳታው የቀረበው በግብፅ የልማት አጋርነት ኤጀንሲ አማካይነት መሆኑ ተመላክቷል።

እንደ ሚኒስቴሩ ገለፃ፤ ይህ ድጋፍ ካይሮ ከኤርትራ ጋር ያላትን “ስትራቴጂያዊና እህትማማች ወዳጅነትን” ለማጠናከር የምታደርጋቸው ጥረቶች አካል ነው።

የህክምና ቁሳቁስ እርዳታው ወደ አስመራ የተላከው፣ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጥቅምት ወር በአስመራ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ነው። ጉበኝቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብር አዲስ ምዕራፍ መሆኑን ሁለቱም ሀገራት ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...