የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በአዲስ አበባ ሁሉም ክ/ከተሞች እና በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ከተሞች ማለትም ፦
– አዳማ
– ቢሾፍቱ
– ዱከም
– ሰበታ
– ቡራዩ
– ሱሉልታ
– ለገጣፎ
– ገላን በሚገኙ 570 የንግድ ተቋማት ላይ ባደረገው ፍተሻ አስገዳጅ የጥራትና የገላጭ ጽሁፍ መስፈርቶችን (CES 73) ያላሟሉ ሕገ-ወጥ ምርቶች በገበያ ላይ መገኘታቸውን ገልጿል።
ህብረተሰቡ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ የሚከተሉትን ምርቶች እንዳይጠቀም ባለስልጣኑ አሳስቧል።
1. የገበታ ጨው (32 ዓይነቶች) ፦ ሰይፋ፣ ቲና፣ እሙሹ፣ ቃሊ፣ አዮዲን፣ እኑ፣ አራዳ፣ ንጉስ፣ ሀሮት፣ ኩል፣ አሜን፣ ሰቦኑማ፣ እቱ፣ መክሊት፣ ዳግም፣ መርሰን፣ ኒሀል፣ ሊቅ፣ ስካይ፣ ናፊ፣ አቤ፣ ሳሮማ፣ ፀሐይ፣ ማሩ፣ ንጉስ፣ እንቁ፣ ሰኒ፣ ሚያዋ፣ ስኬት፣ ሔራል፣ ቤዝ እና ገዳ
2.የምግብ ዘይት (19 ዓይነቶች) ፦ ምስራቅ ፀሐይ፣ ቃል፣ አፍራን፣ ኒያ፣ ሪሃ፣ ኤአይ ሻኪር፣ ኤ1-ኑር፣ ጥራ፣ ረዲ፣ አያን፣ ሳፊያ፣ እሰይ የተጣራ ፣ አማን፣ ላምሮት ኬኬ፣ እድገት፣ ራኒያ፣ ሸገር፣ ሀይላለ እና ፍፁም የተጣራ
3.የለውዝ ቅቤ ፦ ሀራ ፣ ሶራ፣ ብሉ፣ ስዊት ክሬም፣ ሉሲ እና ስንቅ
4. ማር ፦ ቤዛ፣ ውብሸት የማር ጠጅ ፣ ጂጂ፣ አምባሰል እና የኢሉባቦር ማር
5. ከረሜላ ፦: ቡርቃ ሎሊፖፕ፣ አዩ ፓፕ፣ አፍሪ እና ዴሉክሴ ከረሜላዎች፤
ባለስልጣን መ/ቤቱ እነዚህ መስፈርቱን የማያሟሉ፣ በመስሪያ ቤቱ ያልተመዘገቡ፣ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ ሕገ-ወጥ የምግብ ምርቶች ናቸው ፤ ” ህብረተሰባችን እንዳይጠቀማቸው ” ብሏል።
ምርት ሲገዙ ሊሟሉ የሚገቡ መስፈርቶችምንድናቸው ?
– በግልጽ የሚታይ ገላጭ ጽሁፍ ሊኖራቸው ይገባል።
– የአምራች ድርጅት ስም እና ሙሉ አድራሻ።
– የምርቱ የወል ስም ፣ የምርቱ ክብደት፣ የተመረተበትና የሚያበቃበት ቀን።
– መለያ ቁጥር (Batch Number) ችግር ቢገኝ ምርቱ ተለይቶ የሚታወቅበት መለያ።
– አስገዳጅ የጥራት ደረጃ ምልክት።
