ጥበባት ለሀገር ማንነት እና እድገት ቁልፍ ናቸው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

Date:

ጥበባት ለሀገር ማንነት እና እድገት ቁልፍ ናቸው ባሕላዊ ሀብትን ጠብቀው ያቆያሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ጥበባት ለማኅበራዊ አንድነት አበክረው በመስራትም ብዝኃነት ላላቸው ማኅበረሰቦች ድምፅ ይሆናሉ ብለዋል።

በትምህርት ረገድም ጥበባት ፈጠራን እና ምክንያታዊ አስተሳሰብን ያሳድጋሉ። በኢኮኖሚ ረገድም ጥበባት ፈጠራን፣ ቱሪዝምን እና ስራ ፈጠራን የመምራት አቅምም አላቸው ሲሉም ገልጸዋል።

ትላንት ጠዋት ከመላው ኢትዮጵያ ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት ማካሔዳቸውን ገልጸዋል።

ተወካዮቹ በተለያየ ደረጃ እየተካሄደ በመጣውና በዘርፉ ያሉ ቁልፍ ጉዳዮችን ለመለየት በረዳው ሰፊ የውይይት መርሃ-ግብር የተሳተፉ ናቸው ብለዋል።

መድረኩም የውይይት ግኝቶቹን በማጠናከር የከፍተኛ አመራሩን ትኩረት እና መፍትሔ የሚሹ እንዲሁም በዚህ መስክ የተሰማሩ አካላት ሚናቸውን የሚወጡባቸው ጉዳዮችን በመለየት ላይ ያተኮረ ነበር ሲሉም ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...